አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲስ የሚደራጀው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እና በነባሩ የደቡብ ክልል የስልጣን ርክክብ አደረጉ።
የደቡብ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 2ኛ አመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ሁለተኛ ቀን ውሎ እየተካሄደ ይገኛል።
በዛሬው ውሎው የተወያየበትን በክልሎቹ መካከል የሚኖረውን አስተዳደራዊና ህጋዊ ጉዳዮች የሚመራበትን ሥርዓት በተመለከተ የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ (ሞሽን) መርምሮ አጽድቋል።