የሀገር ውስጥ ዜና

ክልሎቹ የስልጣን ርክክብ አደረጉ

By Amare Asrat

August 05, 2023

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲስ የሚደራጀው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እና በነባሩ የደቡብ ክልል የስልጣን ርክክብ አደረጉ።

የደቡብ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 2ኛ አመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ሁለተኛ ቀን ውሎ እየተካሄደ ይገኛል።

በዛሬው ውሎው የተወያየበትን በክልሎቹ መካከል የሚኖረውን አስተዳደራዊና ህጋዊ ጉዳዮች የሚመራበትን ሥርዓት በተመለከተ የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ (ሞሽን) መርምሮ አጽድቋል።