የሀገር ውስጥ ዜና

ብርሃኑ ነጋ(ፕ/ር) በአፋር ክልል በትምህርት ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን እየጎበኙ ነው

By Meseret Awoke

August 08, 2023

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ(ፕ/ር) በአፋር ክልል በትምህርት ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን ተዘዋውረው እየጎበኙ ነው።

በአሁኑ ወቅት በክልሉ ሠመራ ከተማ ውስጥ በትምህርት ዘርፉ የተከናወኑ ስራዎችን ተዘዋውረው እየተመለከቱ ይገኛሉ።

ችግኝ በመትከልም አረንጓዴ አሻራቸውን ማኖራቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።

በቀጣይ በክልሉ በትምህርት ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራትን ከክልሉ አመራሮች ጋር በመሆን እንደሚገመግም ይጠበቃል።

በመረሐ-ግብሩ ላይ በክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አሚና ሴኮ፣ የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አብዱ ሀሰን እንዲሁም የገጠር መሬት አስተዳደር እና አካባቢ ጥበቃ ቢሮ ኃላፊ አህመድ ኢብራሂም ተገኝተዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!