አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) “የኢትዮጵያ ህዝብ እንዳሁኑ ያሉ ፈታኝ ጊዜያትን ሲያልፍ የመጀመሪያው አይደለም፤ ትብብር ካለ ፈተናውን መሻገር ይቻላል” አሉ የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግና የኮቪድ 19 ብሄራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል ወይዘሮ አዳነች አቤቤ።
ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በዛሬው እለት የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የሚያስችል ክሮፕሴቭ ከተባለ የግል ድርጅት የተበረከተ የፀረ ተህዋሲሃን መርጫ መሳሪያዎችን ድጋፍን ተረክበዋል።