አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 6 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አቶ ቀጀላ መርዳሳ በሐረር ከተማ በመገኘት የክረምት በጎ ፈቃድ ስራን አስጀምረዋል።
በዚህ ወቅት የአቅደ ደካማ መኖሪያ ቤቶች እድሳትን ያስጀመሩ ሲሆን፥ የችግኝ ተከላ መርሐግብርም ተካሄዷል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የሐረሪ ክልል የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተግኝተዋል ።
ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት በጎ ፈቃድኝነት የተባረከ ስራ መሆኑን ጠቅሰው፥ ቤቶቹ በቅርብ ጊዜ ተጠናቀው ለነዋሪዎች እንደሚተላለፉ ተናግረዋል።
በምንያህል መለሰ