RemasterDirector_18da6b0cf

የሀገር ውስጥ ዜና

በሶማሌ ክልል ለታማኝ ግብር ከፋዮች እውቅና ተሰጠ

By Melaku Gedif

August 14, 2023

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 8 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሌ ክልል ለታማኝ ግብር ከፋዮች የእውቅና እና ሽልማት መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡

በመርሐ ግብሩ ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሃመድ፣ የፌዴራል እና የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች እንዱሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

አቶ ሙስጠፌ÷ በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ ውጤታማ መሰረተ ልማቶች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ግብርን በአግባቡ መክፈልና መሰብሰብ መሳኝ መሆኑን አንስተዋል፡፡

በክልሉ በ2016 በጀት ዓመት 16 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን ጠቁመው÷ ገቢውን ስኬታማ ለማድረግ ዕውቅና ያገኙ ግብር ከፋዮች የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

በሶማሌ ክልል በ2015 የበጀት ዓመት 9 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 9 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር መሰብሰብ መቻሉ ተጠቁሟል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በ2016 በጀት ዓመት የታቀደው ገቢ በስኬት ለመሰብሰብ በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ መናገራቸውን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡