የሀገር ውስጥ ዜና

ፕሬዚዳንቱ የኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማሳደግ ቁርጠኝነታውን በድጋሚ አረጋገጡ

By Meseret Awoke

August 17, 2023

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ፕሬዚዳንት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማሳደግ ቁርጠኝነታውን በድጋሚ አረጋገጡ፡፡

በተባበሩት አረብ ኢምሬቶች የኢትዮጵያ አምባሳደር ዑመር ሁሴን የሹመት ደብዳቤያቸውን በቤተመንግስት በተካሄደ ሥነስርዓት ላይ ለፕሬዚዳንቱ አቅርበዋል፡፡

ፕሬዚዳንቱ የእንኳን ደህና መጡ መልዕክታቸውን ለአምባሳደሩ ገልጸው፤ መንግስታቸው ለአምባሳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

አክለውም፥ ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ እና የኢትዮጵያ ህዝብ ላቀረቡላቸው መልካም ምኞትም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በዚህ ወቅትም የሀገራቱን የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማጠናከር ጠንክሮ መስራት እንደሚያስፈልግም ነው የተናገሩት፡፡

ሀገራቸው እስካሁን በኢትዮጵያ ትኩረት ተሰጥቶ ያልተሰራባቸው ዘርፎች ላይ በመሰማራት የሁለትዮሽ ግንኙነቷን ለማሳደግ ያላትን ቁርጠኝነት ገልጸዋል፡፡

በዚህም ሀገሪቱ ፥ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ፣ የኢንዱስትሪ፣ የግብርና እና የቱሪዝም ዘርፎችን ላይ ትኩረት አድርጋ እንደምትሰራ ገልጸዋል፡፡

#Ethiopia #saudiarabia #bilateral

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!