የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ ለቡሄ በዓል ርችት መተኮስ ክልክል መሆኑን ፖሊስ አስታወቀ

By Melaku Gedif

August 18, 2023

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቡሄ በዓልን ምክንያት በማድረግ በሚከናወነው የችቦ ማብራት ስነ ስርዓት ርችት መተኮስ ክልክል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ፖሊስ ጉዳዩን አስመልክቶ ባስተላለፈው መልዕክት÷የከተማዋን ሰላም በዘላቂነት ለማረጋገጥ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልጿል፡፡

ይህንኑ የፀጥታ ስራ በአግባቡ ለመምራትና ለመቆጣጠር ሲባል እንዲሁም አጋጣሚውን በመጠቀም ሊፈፀሙ የሚችሉ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል በቡሄ በዓል ርችት መተኮስ መከልከሉ ተጠቁሟል፡፡

ሕብረተሰቡም ይህን ተገንዝቦ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል፡፡