የሀገር ውስጥ ዜና

በደቡብ ክልል አሌ ልዩ ወረዳ በደረሰ የመሬት ናዳ የ12 ሰዎች ህይወት አለፈ

By Tibebu Kebede

May 09, 2020

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 1፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል አሌ ልዩ ወረዳ ጎሮዜ ቀበሌ ትናንት በተከሰተ የመሬት ናዳ የ12 ሰዎች ህይወት አለፈ።

ህይወታቸው ካለፈ ሰዎች መካከልም እስካሁን የ5 ሰዎች አስከሬን መገኘቱ ነው የተገለፀው።