የሀገር ውስጥ ዜና

የዓለም ባንክ ሥደተኞችን በተመለከተ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠየቀ

By Alemayehu Geremew

August 23, 2023

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ባንክ ለሥደተኞች እና ሥደተኞችን ለሚያስተናግዱ ማኅበረሰቦች የሚያደርገውን ድጋፍ ይበልጥ እንዲያጠናክር የሥደተኞች እና ከሥደት ተመላሾች አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል ጠይባ ሐሰን ጠየቁ፡፡

ዳይሬክተር ጀነራል ጠይባ ሐሰን ÷ በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ከፍተኛ ኦፊሰር ከሆኑት ሞሐመድ ከድር አብዴል-ራዚግ ጋር ተወያይተዋል፡፡

ባንኩ በድጋፍ በኩል እስካሁን ላበረከተው ከፍተኛ አስተዋፅዖም በመርሐ-ግብሩ ላይ ማመስገናቸው ተገልጿል፡፡

በቀጣይም አገልግሎቱ ይበልጥ የተሻለ ምላሽ ይሰጥ ዘንድ የዓለም ባንክ ድጋፉን እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።

በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ከፍተኛ ኦፊሰር ሞሐመድ ከድር አብዴል-ራዚግ በበኩላቸው ÷ የዓለም ባንክ ከኢትዮጵያ መንግስት እንዲሁም ከሥደተኞች እና ከሥደት ተመላሾች አገልግሎት ጋር በትብብር መሥራቱን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡

ኢትዮጵያ ሥደተኞችን በማስተናገድ ረገድ እየተወጣች ያለውን ሚና አድንቀው የዓለም ባንክ ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል፡፡