የሀገር ውስጥ ዜና

የዓለም ጤና ድርጅት ለተሃድሶ ኮሚሽን ድጋፍ ማድረግ በሚችልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተካሄደ

By Melaku Gedif

August 24, 2023

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ከዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ ምክትል ተወካይ ድላሚኒ ሮዝ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም የዓለም ጤና ድርጅት ለተሃድሶ ኮሚሽን ድጋፍ በሚያደርግባቸው ሁኔታዎች ላይ መምከራቸውን አምባሳደር ተሾመ ቶጋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

በተለይም ድርጅቱ የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ላይ በትብብር መስራት በሚችልባቸው ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን ጠቁመዋል፡፡