የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ በተለያዩ መሥኮች እንሰራለን አሉ

By Alemayehu Geremew

August 29, 2023

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ በንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ጸጥታ ጉዳዮች ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ፡፡

በናይጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር አዋል ዋግሪስ መሐመድ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ቦላ አሕመድ ቲኑቡ አቅርበዋል።

በዚህ ወቅትም ፥ የሀገራቱ ታሪካዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የበለጠ መጠናከር በሚችልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውንም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በናይጄሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደር አዋል ዋግሪስ ሞሐመድ ÷ ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያላትን የሁለትዮሽና የባለ-ብዙ ወገን ትብብር የበለጠ ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኗንም ገልጸዋል።

ፕሬዚዳንቱ በበኩላቸው ፥ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር በንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።