የሀገር ውስጥ ዜና

ከሐሰተኛና ሕገ ወጥ የገንዘብ ዝውውር ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

By ዮሐንስ ደርበው

August 29, 2023

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ቢራ ሰፈር በግለሰብ መኖሪያ ቤት 200 ሺህ ሐሰተኛ ብር እና 700 የአሜሪካ ዶላር ተይዟል፡፡

ከዚሁ ወንጀል ጋር በተያያዘም ሁለት ተጣርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራው እየተጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ መረጃ ያመላክታል፡፡

በዓላት ሲቃረቡ ሐሰተኛ ብርን ወደ ሕብረተሰቡ ለማሰራጨት እንቅስቃሴ እንደሚደረግ ያስታወሰው ፖሊስ፥ ሕብረተሰቡ በግብይት ወቅት ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስቧል፡፡

አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙም ለፀጥታ አካላት ጥቆማ መስጠት እንደሚያስፈልግ ነው ያስገነዘበው፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!