<p>South Korean President Moon Jae-in, second from left, meets with medical members at the Daegu Medical Center in Daegu, South Korea, Tuesday, Feb. 25, 2020. China and South Korea on Tuesday reported more cases of a new viral illness that has been concentrated in North Asia but is causing global worry as clusters grow in the Middle East and Europe. (Bae Hun-shik/Newsis via AP)</p>

ዓለምአቀፋዊ ዜና

ዳግም ያገረሸው የደቡብ ኮሪያ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስጋት ፈጥሯል

By Tibebu Kebede

May 11, 2020

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 3፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ኮሪያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ዳግም እያንሰራራ መሆኑ ተነገረ።

በሀገሪቱ ዛሬ ብቻ 35 ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸው፤ በአጠቃላይ በ48 ሰዓታት ውስጥ በሀገሪቱ 69 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው ነው የተገለፀው።

አብዛኛዎቹ ሰዎችም ቫይረሱ ያገኛቸው በመዲናዋ በሚገኙ የምሽት ዳንስ ቤቶች እና ባሮች መሆኑ ተመልክቷል።

እስካሁን 4 ሺህ ሰዎች በእንደነዚህ ሰፍራዎች ላይ የነበሩ ሰዎች የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገላቸው ሲሆን፥ ቀሪ 3 ሺህ ሰዎችን የማሰሱ ስራ መቀጠሉ ተገልጿል።

የሀገሪቱ መንግስትም ዋና ትኩረቱ እነዚሀን ሰዎች አድኖ በመያዝ ምርመራ ማድረግ መሆኑን አስታውቋል።

በተመሳሳይ በቻይናም አዳዲስ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ ነው የተሰማው።

ባለፉት ሰዓታት ሀገሪቱ 17 ሰዎች ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ስትገልፅ ከእነዚህ ውስጥ አምስቱ በዉሃን ግዛት የሚገኙ የአንድ መንደር ሰዎች ናቸው።