የሀገር ውስጥ ዜና

የኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ ቦታዎች ከአሸባሪው ሸኔ ነፃ መሆናቸው ተገለጸ

By ዮሐንስ ደርበው

August 30, 2023

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሸባሪው ሸኔ ቡድን አባላት በስፋት ሲንቀሳቀስባቸው የነበሩ የኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ከቡድኑ የሽብር እንቅስቃሴ ነፃ መሆናቸውን ዘመቻውን የሚመሩ ከፍተኛ የሰራዊቱ መኮንኖች ተናገሩ፡፡

ቡድኑ ህብረተሰቡን ለመዝረፍ እና የትራንስፖርት መስመሮችን ለመዝጋት የሚጠቀምባቸው እንዲሁም ለሽብር ስራው ምቹ የነበሩ ቦታዎች ነፃ ማድረግ መቻሉን ነው ከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮች ያስታወቁት፡፡

የዘመቻው የከባድ መሳሪያ ምድብተኞች በበኩላቸው÷ በሸኔ ላይ እየተወሰደ በሚገኘው እርምጃ ኃላፊነታቸውን በብቃት እየተወጡ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የሚሰጣቸውን ማንኛውም ተልዕኮ በከፍተኛ ሞራል እና ተነሳሽነት በመፈፀም ላይ መሆናቸውን የመከላከያ ሠራዊት መረጃ ያመላክታል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!