የሀገር ውስጥ ዜና

የናይጄሪያ ባለሐብቶች በኢትዮጵያ መዋዕለ-ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ሥምምነት ላይ ተደረሰ

By Alemayehu Geremew

September 01, 2023

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የናይጄሪያ ባለሐብቶች በኢትዮጵያ መዋዕለ-ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ሥምምነት ላይ ተደረሰ፡፡

ባለሐብቶቹ በኢትዮጵያ ከሚገኙ አቻ ተቋማትና ባለሐብቶች ጋር ተገናኝተው እንዲሠሩ ሁኔታዎች እንደሚመቻችላቸው መገለጹን በሌጎስ በተካሄደው ዓለምአቀፍ የንግድ ጉባዔ ላይ የተሳተፈው አቡጃ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመላክቷል፡፡

ኤምባሲው በንግድ ጉባኤ ተሳትፎው ለኢትዮጵያ የወጪ ምርቶች ገበያ ማፈላለግ የሚያስችል ሁኔታ ማመቻቸቱን ጠቁሟል፡፡