የሀገር ውስጥ ዜና

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል “የመስዋዕትነት” ቀን እየተከበረ ነው

By ዮሐንስ ደርበው

September 07, 2023

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል “የመስዋዕትነት” ቀን በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ነው።

ቀኑ እየተከበረ የሚገኘው “በመስዋዕትነት የምትጸና ሀገር!” በሚል መሪ ሐሳብ ነው፡፡

ስለሀገርና ሕዝብ መሥዋዕትነት የከፈሉ ጀግኖችን በማስታወስና ክብር በሚሰጡ ሁነቶች ቀኑ እየተከበረ መሆኑን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡

በአከባበሩ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የመከላከያ ሠራዊት፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የክልሉ ፖሊስ እና የጸጥታ አመራሮች እንዲሁም የአሶሳ ከተማ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

በአሶሳ ከተማ በክልሉ ፖሊስ ማርች ባንድ የታጀበ የእግር ጉዞ እየተደረገ መሆኑም ተመላክቷል፡፡

በጉዞው ላይ “መነሻና መድረሻችን የኢትዮጵያ ክብር ነው”፣ “እንደቀደምት አባቶቻችን እኛም ኢትዮጵያችን ከፍ እናደርጋታለን” የሚሉ እና ሌሎች መልዕክቶች እየተላለፉ ይገኛል።

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!