የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ መንግስት ያስቀመጠውን የክፍያ መመሪያ ለተላለፉ 21 የግል ትምህርት ቤቶች የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ተሰጠ

By Tibebu Kebede

May 12, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) መንግስት ያስቀመጠውን የክፍያ መመሪያ ለተላለፉ 21 የግል ትምህርት ቤቶች የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ስልጠና ጥራት ሙያ ብቃትና ምዘና ማረጋገጫ ባለስልጣን አስታወቀ።

የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሸዊት ሻንካ በሰጡት መግለጫ፥ የኮረና ቫይረስ ወረርሽኝን ተከትሎ ከመጋቢት 7 2012 ዓ.ም ጀምሮ በሀገር አፍ ደረጃ ትምህርት መዘጋቱን አስታውሰው፤ የግል ትምህርት ቤቶች በትምህርት ሚኒስተር ውሳኔ መሰረት ክፍያ እንዲቀበሉ መደረጉን ገልፀዋል።