የሀገር ውስጥ ዜና

በ24 ሰዓት ውስጥ በተደረገ 2 ሺህ 424 የላብራቶሪ ምርመራ 11 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው

By Tibebu Kebede

May 12, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 2424 የላብራቶሪ ምርመራ አስራ አንድ (11) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ፥ የሁሉም እድሜያቸው ከ19 እስከ 47 ዓመት የሆኑ ወንዶች መሆናቸውን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ አስታውቅዋል።