የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ ለፀጥታ አካላት የእውቅና መስጠት መርሐ- ግብር ተከናወነ

By Meseret Awoke

September 07, 2023

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ለፀጥታ አካላት የእውቅና መስጠት መርሐ- ግብር ተከናወነ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ጳጉሜን 2 – የመስዕዋትነት ቀንን በማስመልከት መልዕክት አስተላፈዋል፡፡

በመልዕክታቸውም፥ የመዲናዋን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ በታማኝነትና በቅንነት ሲያገለግሉ የህይወትና የአካል መስዋዕትነት ለከፈሉ የፀጥታ አካላት የእውቅና መርሐ- ግብር መከናወኑን ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ በብዙ መስዋዕትነት የጸናች ሀገር ናት ሲሉም ገልጸዋል።

አክለው እንዳሉትም፥ ለራሳችሁ ህይወት ሳትሰስቱ ለሀገራችሁ ክብርና ለህዝባችሁ ሰላምና ደህንነት መስዋዕት በመሆን ዋጋ ለከፈላችሁ ሁሉ በሰላም ወጥተን መግባታችን የእናንተ የመስዋዕትነት ውጤት ነውና ኢትዮጵያ ታመሰግናችኋለች ብለዋል::

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!