የሀገር ውስጥ ዜና

አስተዳደሩ በጃፓን ድጋፍ የተገዙ 79 ማሽኖችን ተረከበ

By ዮሐንስ ደርበው

September 09, 2023

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጃፓን መንግስት በሰጠው ድጋፍ የተገዙ 79 ለመንገድ ጥገና የሚያገለግሉ ማሽኖችንና ከባድ ተሽከርካሪዎች መረከቡን አስታወቀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ÷ “ለከተማችን ሁሉን አቀፍ ልማት የላቀ ፋይዳ ያላቸውን ዘመናዊ ሰፋፊ መንገዶችን እየገነባንና እያሰፋን ባለንበት ወቅት የተደረገልን ድጋፍ ትልቅ ፋይዳ አለው” ብለዋል::

የጃፓን መንግስት እና ሕዝብ እንዲሁም የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ ላደረጉልን ድጋፍ በከተማ አስተዳደራችን ስም እናመሰግናለን ሲሉ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!