የሀገር ውስጥ ዜና

“የአብሮነት ቀን” በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው

By Shambel Mihret

September 11, 2023

አዲስ አበባ፣ ጷጉሜን 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጷጉሜን 6 “የአብሮነት ቀን” በተለያዩ መርሐ ግብሮች በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ነው፡፡

የጷጉሜን 6 የአብሮነት ቀን”“በህብር የተሰራች ሀገር”በሚል መሪ ሀሳብ ነው በመንግሥት እና በግል ተቋማት እየተከበረ የሚገኘው፡፡

የቀኑ መከበርም የአብሮነት እሴትን ለማጎልበት፣ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትና አንድነትን ለማጠናከር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል፡፡