የሀገር ውስጥ ዜና

የሲዳማ ክልል ለ1 ሺህ 205 ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ

By Melaku Gedif

September 11, 2023

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልላዊ መንግስት ለ1 ሺህ 205 ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን አስታወቀ፡፡

የክልሉ ፍትሕ ቢሮ ሃላፊ አቶ ማቶ ማሩ እንደገለፁት÷ የክልሉ ርዕሰ መስተደድር የኢትዮጵያውያን አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ለታራሚዎቹ ይቅርታ አድርገዋል።

ይቅርታ ከተደረገላቸው ታራሚዎች መካከል 12ቱ ሴቶች መሆናቸውን ደሬቴድ ዘግቧል፡፡

ታራሚዎቹ የተለያዩ ወንጀሎችን በመፈፀም ወደ ማረሚያ ተቋማት ገብተው እንደነበር ጠቅሰው÷ በቆይታቸውም መልካም ስነ ምግባር ያሳዩ እንደሆኑም አስረድተዋል።

በይቅርታ የተለቀቁ ታራሚዎች የበደሉትን ህብረተሰብና መንግስት እንዲክሱ፤ ህብረተሰቡም ታራሚዎችን ተቀብሎ ድጋፍ እንዲያደርግ ሃላፊው ጥሪ አቅርበዋል፡፡