የሀገር ውስጥ ዜና

በወላይታ ሶዶ የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ላብራቶሪ ስራ ጀመረ

By Tibebu Kebede

May 13, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በደቡብ ክልል ህብረተሰብ ጤና ተቋም ሁለተኛው የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ላብራቶሪ በወላይታ ሶዶ ስራ ጀመረ፡፡

የላብራቶሪ ምርመራ በቅርቡ በሀዋሳ ከተማ አገልግሎት መስጠት የተጀመረ ሲሆን አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግና በማፋጠን በአንድ ጊዜ የ96 ሰዎችን እና በ24 ሰዓታት ውስጥ የ1500 ሰዎችን ናሙና መመርመር የሚያስችል የወላይታ ሶዶ የላቦራቶሪ ምርመራ አገልግሎት በይፋ መጀመሩን የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ አቅናው ካውዛ ገልጸዋል፡፡