የሀገር ውስጥ ዜና

በፀጥታ ችግር ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ወደ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ገቡ

By Mikias Ayele

September 20, 2023

አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በፀጥታ ምክንያት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ሳይወስዱ የቆዩ ከ11 ሺህ 581 ተማሪዎች የሀገር አቀፍ  ፈተናቸውን ለመውሰድ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ገብተዋል፡፡

የጎንደር ዩኒቨርሲቲም ተማሪዎቹን ለማስፈተን ዝግጅት ማደረጉን አስታውቋል፡፡

ተፈታኝ ተማሪዎች÷ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ፈተናቸውን ማጠናቀቅ አለመቻላቸውን በማስታወስ በአሁኑ ወቅት ፈተናውን ለመውሰድ ሙሉ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

ተማሪዎቹ ያቋረጧቸውን የኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂና ሲቪክስ የትምህርት አይነቶችን ብሄራዊ  ፈተና ይወስዳሉ  መባሉን አሚኮ ዘግቧል፡፡