አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙርያ አለም አቀፉ ማህበረሰብ በግብፅ ያረጀ አስተሳሰብ ቅስቀሳ የተሳሳተ ግንዛቤ እንዳይፈጠርበት ለማድረግ የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ መሆናቸውን በአሜሪካ እና እንግሊዝ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ምሁራን ተናገሩ።
የምጣኔ ሀብት እና የግጭት አፈታት ተመራማሪ የሁኑት ፕሮፌሰር ተሾመ አበበ እና ዶክተር ልዑልሰገድ አበበ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በኢንተርኔት ባደረጉት ውይይት የግብፅ ፔንዱለማዊ ዥዋዥዌ ተቀባይነት የለውም ብለዋል።