ዓለምአቀፋዊ ዜና

በደቡብ አፍሪካ በጆሃንስበርግ ብቻ 1 ሚሊየን ቤተሰቦች የሚመገቡት የላቸውም

By Meseret Awoke

May 14, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 6፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ብቻ 1 ሚሊየን ቤተሰቦች የሚመገቡት ነገር እንደሌላቸው የከተማዋ ከንቲባ ገለፁ።

ጆሃንስበርግ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ለስድስት ሳምንታት ተዘግታ እንደቆየች ነው።

በከተማዋ የንግድ ተቋማት በመዘጋታቸውም በርካታ ሰዎች ስራ አጥተው የሚመገቡትን ለመግዛት እንዳዳገታቸው ይነገራል።

ይህንንም ተከትሎ በከፋ ሁኔታ የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥር አሻቅቧል።

ምንጭ፦ አልጀዚራ