የሀገር ውስጥ ዜና

ሀገራዊ እምቅ አቅማችንን ለመጠቀም ብዙ ዕድሎች አሉን – ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

By ዮሐንስ ደርበው

September 23, 2023

አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኅብረት ለመሥራት ከወሰንን ሀገራዊ እምቅ አቅማችንን ለመጠቀም በብዙ አፅናፋት ብዙ ዕድሎች አሉን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው እንደገለጹት÷ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ የቱሪዝም መዳረሻ ልማት አቅም ያላቸው ወደ 70 የሚጠጉ ደሴቶች መገኛ ሆኗል፡፡

በኅብረት ለመሥራት ከወሰንን ሀገራዊ እምቅ አቅማችንን ለመጠቀም በብዙ አፅናፋት ብዙ ዕድሎች አሉን ሲሉም ገልጸዋል፡፡