የሀገር ውስጥ ዜና

በምዕራብ ጉጂ ዞን በደረሰ የጎርፍ አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ

By Feven Bishaw

May 15, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን ገላና ወረዳ በደረሰ የጎርፍ አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ።

ህይወታቸው ካለፈው ሰዎች በተጨማሪም 8 ሺህ 929 አባዎራዎች እና 63 ሺህ ቤተሰቦች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል ነው የተባለው።