አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 9 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ኢትዮጵያውያን እና በኢትዮጵያ የሚገኙ ሁሉ ለአፍታም ሳይዘናጉ በኮሮና ቫይረስ ዙሪያ የወጡትን መመሪያዎች እንዲተገብሩ አሳሰቡ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በፌስ ቡክ ገፃቸው ላይ ባስተላፉት መልዕክት ቫይረሱን ለመከላከል ልንወስዳቸው የሚገቡ ርምጃዎች አካላዊ ርቀትን መጠበቅ፣ እጆችን ቶሎ ቶሎ በመታጠብ በንጽሕና መያዝ፣ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብልን በአግባቡ መጠቀም እና ለተወሰነ ጊዜ በቤት የሚቆይበትን ደንብ ተግባራዊ ማድረግን ይጨምራል ብለዋል፡፡