የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያና ብሪክስ መካከል ኢኮኖሚያዊ ትብብርን የሚያጠናክር ውይይት ተካሄደ

By Melaku Gedif

October 11, 2023

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያና ብሪክስ አባል ሀገራት መካከል ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡

በሕንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ደመቀ አጥናፉ ከብሪክስ ንግድና እና ኢንዱስትሪ ም/ቤት መስራች ማዱካር (ዶ/ር) እና ምክትል መስራች ሱሺ ሲንግ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷በኢትዮጵያና በብሪክስ አባል ሀገራት መካከል ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም በኢትዮጵያና በብሪክስ መካከል የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትስስርን ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን የኤምባሲው መረጃ ያመላክታል፡፡