በአዲስ አበባ ማዕከል ስልጠናቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ አመራሮች የከተማዋን ግዙፍና ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች በዘጋቢ ፊልም የተመለከቱ ሲሆን አንዳንዶችንም በአካል በመጎብኘት ልምድ እንዲቀስሙ እየተደረገ ነው።
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ስልጠናው ጠንካራ ፓርቲ በመገንባት መንግስትን ለማጠናከር በጊዜ ቀመር የተቀመጡ የፓርቲያችንን ራዕይዎች ለማሳካት እርስ በእርስ መማማርን ዓላማው አድርጎ እየተካሄደ መሆኑን አስገንዝበዋል።
በተመሳሳይ በአርባ ምንጭ ማዕከል ያሉ ሰልጣኞች÷ በጋሞ ልማት ማህበር የአርባምንጭ ግብርና ልማት እንቅስቃሴን ጎብኝተዋል፡፡
እንዲሁም የጅግጅጋ የስልጠና ማዕከል ስልጠኞች በሶማሌ ክልል ፋፈን ዞን በሸበሌ የሚገኝ ዘመናዊ የግመል እርባታ ካምፕን ፣ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው ዶሮ እርባታ ፣ የቱሉ ጉሌድ እርሻ ፣ የፋፈን የእርሻ ማሳ እና የተሰሩ የውሃ መሠረተ ልማት ጎብኝተዋል፡፡