የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል የክፍያ አማራጮች ከ1 ትሪሊየን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር ተከናወነ

By Mikias Ayele

October 28, 2023

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል የክፍያ አማራጮች ባለፉት ሦስት ወራት ከ1 ነጥብ 3 ትሪሊየን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር መከናወኑ ተመላከተ፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2016 (2023/24) በጀት ዓመት የ1ኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ እየተካሄደ ነው፡፡

በጉባዔው እንደተገለጸው÷ ባለፉት ሦስት ወራት አበረታች የዲጂታል የባንክ አገልግሎት የሥራ አፈፃፀም ተመዝግቧል፡፡

በባንኩ ዲጂታል አማራጮች በተከናወኑ ከ245 ሚሊየን በላይ የገንዘብ ዝውወሮች ከ1 ነጥብ 3 ትሪሊየን በላይ የሆነ የብር መጠን መንቀሳቀሱን የባንኩ መረጃ ያመላክታል፡፡