የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያና ኖርዌይ በደን ልማት አስተዳደር ላይ በትብብር ለመስራት ተወያዩ

By Melaku Gedif

November 01, 2023

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ ከኖርዌይ አምባሳደር ስቲያን ክሪስተንሰን ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ኢትዮጵያ እና ኖርዌይ በግብርናው ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡

በተለይም በዘላቂ ደን ልማት አስተዳደር ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና የተራቆቱ አካባቢዎችን መልሶ በማልማት ላይ በትብብር በቅንጅት ለመስራት ተወያይተዋል፡፡

በተጨማሪም የዜጎችን ሕይወት ማሻሻል በሚያስችሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ግቦች ዙሪያ መምከራቸውን አምባሳደሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡