የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ አወል አርባ በአዋሽ ፈንታሌ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ

By ዮሐንስ ደርበው

November 03, 2023

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝታቸውም በአካባቢው እየለማ የሚገኘውን የፓፓዬ ምርት እና ሌሎች ሥራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡

አቶ አወል በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት÷ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፡፡

ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት የሚደረገው ጥረት አበረታች እንደሆነም በማህበራዊ ትሥሥር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡