የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ ደመቀ መኮንን ከታንዛንያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

By Meseret Awoke

November 09, 2023

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከታንዛንያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጃንዋሪ ማካምባ ጋር በስልክ ተወያይተዋል፡፡

ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው በኢትዮጵያ እና ታንዛኒያ ቀጣናዊ የጋራ ፍላጎት ዙሪያ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መረጃ ያመላክታል፡፡

በአፍሪካ ሕብረት ጉዳዮች ፣ በከፍተኛ መሪዎች ደረጃ በሚካሄድ ጉብኝት እና ስለቀጣዩ የሁለቱ አኀራት የጋራ ሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ዙሪያም ተወያይተዋል።

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!