አዲስ አበባ፣ ሕዳር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን የግንባታ ዘርፉን አቅም የሚያጎለብቱ ፕሮጀክቶች አስመርቋል፡፡
በምርቃት ስነ- ስርዓቱ ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የመከላከያ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)ን ጨምሮ ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ሃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
ኮርፖሬሽኑ ዛሬ ለምረቃ ካበቃቸው ፕሮጀክቶች መካከል የግንባታ ባለሙያዎች ልማት ኢኒስቲትዩት ፣ የግንባታ ኢንዱስትሪዎች ግብዓት ማምረቻና ማከፋፈያ እንዲሁም ቢውልዲንግ ኢንፎርሜሽን ሞዴሊንግ ይገኙበታል ።
ከዚህ ባለፈም ኮርፖሬሽኑ ያለፈባቸውን ሂደቶች የሚያስቃኙ የፎቶግራፍ አውደ- ርዕይ ለጎብኚዎች ክፍት መደረጉም ነው የተገለጸው።
ተቋሙ በ10 ዓመቱ ከያዛቸው የልማት ፕሮግራሞች ውስጥ የግንባታ ዘርፍ አንዱ ሲሆን ፥ ዘርፉን በሰው ሃይልና ቴክኖሎጂ ተወዳዳሪ እንዲሆን እየሰራ እንደሆነ ተነስቷል።
ዛሬ ለምርቃት የበቁት ፕሮጀክቶች በመስኩ የተሻለ ስራ ለመከናወን ተጨማሪ አቅም የሚፈጥሩ መሆናቸውም ነው የተነሳው፡፡
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!