የሀገር ውስጥ ዜና

የብልጽግና ፓርቲ ልዑካን ቡድን በቻይና የመስኖ ፕሮጀክትን ጎበኘ

By Meseret Awoke

November 15, 2023

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ የተመራ ከፍተኛ ልዑክ በቻይና የዱጂያንግያን የመስኖ ፕሮጀክትን ጎብኝቷል፡፡

የመስኖ ፕሮጀክቱ ጎርፍን ለመከላከል፣ ለቼንዱ አካባቢ የመስኖ ውሃ ምንጭ ለመሆን እና ለቱሪስት መዳረሻነት ለማገልገል እንደሚሆን ተገልጿል፡፡

ይሕም ጥንታዊ የቻይና ጥበብ እና የምህንድስና ችሎታን የሚወክል እንደሆነም መነሳቱን በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመልክቷል።

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!