አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የለይቶ ማቆያ ቦታዎች ንኡስ ኮሚቴ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀው የለይቶ ማቆያ ቦታ የተለያዩ አገልግሎት ለሚሰጡ ሠራተኞች የበዓል ስጦታ አበረከተ።
የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤና የሴቶች ሕፃናትና ወጣቶች ሚኒስትር ወይዘሮ ፊልሰን አብዱላሂ ትላንት ማምሻውን በቦታው ተገኝተው ሠራተኞቹን ለሚያደርጉት ጥረት አመስግነዋል።