የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለይቶ ማቆያ ለሚያገለግሉ ሠራተኞች የበዓል ስጦታ ተበረከተ

By Tibebu Kebede

May 23, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የለይቶ ማቆያ ቦታዎች ንኡስ ኮሚቴ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጀው የለይቶ ማቆያ ቦታ የተለያዩ አገልግሎት ለሚሰጡ ሠራተኞች የበዓል ስጦታ አበረከተ።

የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤና የሴቶች ሕፃናትና ወጣቶች ሚኒስትር ወይዘሮ ፊልሰን አብዱላሂ ትላንት ማምሻውን በቦታው ተገኝተው ሠራተኞቹን ለሚያደርጉት ጥረት አመስግነዋል።