አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም እና በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞኖች የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የወጣውን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተላልፈው የተገኙ ከ5 ሺህ በላይ ሰዎች በገንዘብና እስራት እንዲቀጡ መወሰኑ ተገለጸ።
የምስራቅ ጎጃም ዞን ኮሮና መከላከል ግብረ ኃይል የኮሙዩኒኬሽን እና ሚዲያ አባል ኮማንደር ራሄል አብርሃም፥ እንደገለፁት በሁሉም የዞኑ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የአዋጁን የክልከላ ድንጋጌ ለማስከበር ቁጥጥር ሲደረግ ቆይቷል።