የሀገር ውስጥ ዜና

የኮቪድ 19 ወረርሽ አስከፊነት ከግምት ያስገባ የጥንቃቄ እርምጃዎች ተጠናክሮ መቀጠል አለበት- ም/ጠ ደመቀ

By Tibebu Kebede

May 25, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮቪድ 19 ወረርሽ ስርጭት አሳሳቢ እየሆነ በመምጣቱ የችግሩን አስከፊነት ከግምት ያስገባ የጥንቃቄ እርምጃዎች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን አሳሰቡ፡፡

የሚኒስትሮች ኮሚቴ ከኮቪድ-19 አማካሪ ግብረ-ሃይል ጋር በወቅታዊ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስርጭት እና መከላከል ዙሪያ በምስል የተደገፈ ውይይት ተካሄዷል፡፡