የሀገር ውስጥ ዜና

ኮርፖሬሽኑ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ከተመረቱ ምርቶች ከ1 ነጥብ 2 ቢሊየን በላይ ዶላር መገኘቱን አስታወቀ

By ዮሐንስ ደርበው

December 22, 2023

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት አምስት ዓመታት በኢንዱስትሪ ፓርኮች ከተመረቱ ምርቶች ከ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታውቋል፡፡

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በዘርፉ የተሰማሩ ባለሃብቶችን ችግር ለመፍታት ያለመ የባለድርሻ አካላት ፎረም እየተካሄደ ነው፡፡

ፎረሙ÷ ባለድርሻ አካላትን በማሰባሰብ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚያመርቱ ኢንቨስተሮች የሚገጥማቸውን ችግር ለመፍታት፣ እልባት የሚሰጥበት እና አቅጣጫ የሚቀመጥበት እንደሆነ ተመላክቷል፡፡

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ እንዳሉት÷ ባለፉት አምስት ዓመታት በኢንዱስትሪ ፓርኮች ከተመረቱ ምርቶች ከ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።

በኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ከ80 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች የሥራ ዕድል መፈጠሩንም ነው ያስታወቁት፡፡

ኮርፖሬሽኑ አበረታች ሥራዎችን እያከናወነ ቢሆንም በይበልጥ ውጤታማ ለመሆን የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!