አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት ለዓይነ ስውራን የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡
ጽህፈት ቤቱ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ÷ በየዓመቱ ታኅሣስ 26 ቀን የሚከበረው የዓለም የብሬል ቀን ለዓይነ ስውራን ተደራሽነትን እንደሚያስታውስ አመልክቷል፡፡
የብሬል ፈጣሪ የሆነው ሉዊስ ብሬል በዚህ ቀን እንደሚታወስም ነው የገለጸው፡፡
ጽህፈት ቤቱ ፥ ዓይነ ስውራን በየቀኑ ብዙ ፈተናዎች የሚያጋጥሟቸው በመሆኑ በሁሉም አቅጣጫ መደገፍ እና ተካታችነታቸውን ማረጋገጥ ይገባል ብሏል፡፡
የቀዳማዊት እመቤት ፅህፈት ቤት ለብሬል ተጠቃሚዎችም ለዓለም የብሬል ቀን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል፡፡
ለዓይነ ስውራን የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ማረጋገጡንም የጽህፈት ቤቱ መረጃ ያመላክታል፡፡
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- FBC(Fana Broadcasting Corporate S.C.) ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!