የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያና ሶማሊላንድ በልማት እቅዶችና ፍላጎቶች ላይ በጋራ ለመስራት ተስማሙ

By Meseret Awoke

January 06, 2024

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 27፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ከሶማሊላንድ ፕላንና ልማት ሚኒስትር አሕመድ ሞሃመድ ድሪር (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ ሁለቱ ሚኒስትሮች በተለያዩ የልማት ሥራዎች ላይ በትብብር ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡

በተለይም በመሪ የልማት እቅዶች እንዲሁም የልማትና የእድገት ፍላጎቶች መሰረት ባደረጉ ጉዳዮች ላይ በትብብር እንደሚሰሩ ማረጋገጣቸውን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.) ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!