አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 24 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስቴር፣ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እና የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኢንስቲትዩት የማዕድንና ነዳጅ ልማትን ለማፋጠን የሚያስችል የሶስትዮሽ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ።
ስምምነቱ የማዕድንና ነዳጅ ዘርፍን በሳይንስ፣ በጥናትና ምርምር መደገፍ ለሀገራችን ሁለንተናዊ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ታምኖበታል።