የሀገር ውስጥ ዜና

ሰብዓዊ መብት የምናከብረውና የምናስከብረው ለማንም ብለን ሳይሆን ለህዝባችንና ለፍትህ ስንል ነው- ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

By Tibebu Kebede

June 02, 2020

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 25፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) “ሰብዓዊ መብት የምናከብረውና የምናስከብረው ለማንም ብለን ሳይሆን ለህዝባችን እና ለፍትህ ስንል ነው” ሲሉ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ገለፁ።

ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ሰሞኑን አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው ሪፖርት ዙሪያ በፌስቡክ ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት፥ “በአምነስቲ ኢንተርናሽናል የወጣውን መግለጫ ተመልክተነዋል” ያሉት ወይዘሮ አዳነች፥ ሪፖርቱን የማጣራት ስራ መጀመሩንም አስታውቀዋል።