የሀገር ውስጥ ዜና

ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች የምሥራቅ አፍሪካ አርብቶ አደሮች ኤክስፖን ጎበኙ

By ዮሐንስ ደርበው

January 31, 2024

አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ የሚገኘውን የምሥራቅ አፍሪካ አርብቶ አደሮች ኤክስፖን ጎብኝተዋል፡፡

ኤክስፖው “አርብቶ አደርነት የምሥራቅ አፍሪካ ኅብረ ቀለም” በሚል መሪ ሐሳብ በሚሊኒየም አዳራሽ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

በዛሬው ዕለትም የመንግሥት ከፍተኛ ሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ በብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽሕፈት ቤት የሚገኙ አመራሮች ኤክስፖውን ጎብኝተዋል፡፡