አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 26፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ)የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እርስቱ ይርዳ እና የደቡብ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጥላሁን ከበደን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ የስራ ሀላፊዎች በሀላባ ዞን የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ጉበኙ።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ የተመራው ልኡክ በሀላባ ዞን በአቶቲ ኡሎ ወረዳ በየዬ ቀበሌ የበቆሎ ሰብሎችን እና ሌሎች የበልግ አዝመራዎችን ጎብኝተዋል።