የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ ማሞ ምህረቱ ከቪዛ ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጋር ተወያዩ

By Melaku Gedif

February 07, 2024

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ከቪዛ ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሪያን ማኪነርኒ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ ኢትዮጵያ ከቪዛ ኩባንያ ጋር ያላትን አጋርነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡

አዳዲስ የዲጂታል ክፍያ አማራጮችን ማስፋፋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውንም የባንኩ መረጃ ያመላክታል፡፡