አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በምእራብ ኦሮሚያ ዞኖችና የተለያዩ አካባቢዎች በግድያና ዘረፋ ወንጀል ላይ ተሰማርተው የነበሩ 48 ሰዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር እና የወንጀል ክትትል ዘርፍ አዛዥ ግርማ ገላን በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ፥ “አባ ቶርቤ” በሚል ስም ተደራጅተው የሰዎችን ህይወት ሲያጠፉ የነበሩ ግለሰቦብ በተደረገው ፍተሻና ክትትል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል።