የሀገር ውስጥ ዜና

ፖሊስ በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር የተሰማሩ አዘዋዋሪዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ገለጸ

By Shambel Mihret

February 27, 2024

አዲስ አበባ፣ የካቲት 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር የተሰማሩ ሦስት አዘዋዋሪዎችን ጨምሮ 117 ከሀገር ሊወጡ የነበሩ ሰዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የፌደራል ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ከኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በሕገ-ወጥ አዘዋዋሪዎች ተታልለው በሶማሌ ክልል በኩል ከሀገር ሊወጡ ሲሉ ቶጎ ውጫሌ ላይ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውንም ነው ፖሊስ የገለጸው፡፡

የአብዛኞቹ ዕድሜም ከ15 ዓመት አለመብለጡን የፌደራል ፖሊስ መረጃ አመላክቷል፡፡

ሕብረተሰቡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሰው ልጅን ማዘዋወር የሰብዓዊ መብት ጥሰት መሆኑን ተገንዝቦ መሰል ድርጊት ሲመለከት ለፀጥታ አካላት ጥቆማ እንዲሰጥ ተጠይቋል፡፡